ለመጠጥ ውሃ ሳኒቴሽን እና ሀይጂን ብሄራዊ ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል 2 ሚሊዮን 290 ሺህ ዩ.ኤ (ሁለት ሚሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና ሺህ ዩ.ኤ) የሚያስገኘው ተጨማሪ የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በአፍሪካ ልማት ፈንድ መካከል ግንቦት 16 ቀን 2009 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 28 ቀን 2009 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው ስለሆነ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ህገ መንግስት አንቀፅ 55(1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።