ለአራት ከተሞች መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ሳኒቴሽን ፕሮግራም ማስፈፀሚያ የሚውል 76 ሚሊዮን 110 ሺህ የአሜሪካን ዶላር (ሰባ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ አስር ሺህ የአሜሪካን ዶላር) የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፕብሊክ መንግስት እና በአፍሪካ ልማት ባንክ እ.አ.አ. ፌብሩዋሪ 3 ቀን 2016 በአዲስ አበባ የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 27 ቀን 2008 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው ስለሆነ፤
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀፅ 55 (1) እና (12) መሰረት የሚከተለው ታውጇል፡፡