በነጥብ የሥራ ምዘና ዘዴ በተመዘኑ የሥራ መደቦች ላይ የሠራተኞች ድልድል የሚፈጸምበትን የድልድል አፈጻጸም መመሪያ ከግንቦት 1 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ ለሙከራ ትግበራ በተመረጡ ተቋማት ተግባራዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡
በዚህ መሠረት በመመሪያው ላይ በተለያዩ መድረኮች ማብራሪያና መግለጫዎች የተሰጡ ሲሆን፣ አንዳንድ የፌዴራል እና የክልል ተቋማት እያቀረቡ ያሉ ተመሳሳይ ጥያቄዎችን በማሰባሰብ በመመሪያው አንቀጾች ላይ ሁሉም ተቋማት ተመሳሳይ አሠራር እንዲከተሉ ማብራሪያ ማስተላለፍ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
በመመሪያው ላይ የተሰጠውን ተጨማሪ ማብራሪያዎች ከዚህ ጋር አያይዘን መላካችንን እንገልጻለን፡፡