ተቋሙ የደንብ ልብስ፣ የስራ ልብስ እና የአደጋ መከላከያ መሳሪያዎችን ወጥ በሆነ መልኩ እያጠና በወቅቱ ለሰራተኞች እንዲቀርቡ የማድረግ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን በመገንዘብ፤ ተቋሙ ሲጠቀምበት የነበረውን የኢትዮያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባሥልጣን ያወጣው መመሪያ ቁጥር 105/2007 ሲሆን ተቋሙ ከታህሳስ 2010 ዓ.ም ጀምሮ ራሱን ችሎ ስለተደራጀ የራሱን መመሪያ ማውጣት በማስፈለጉ የነበረው መመሪያም የራሱ ውሰንነቶች ሰለነበሩት ፤ የቅሬታ ምንጭ ስለነበሩትና ተቋሙ በ2011 ዓ፣ም ባስጠነው የመሠረታዊ የስራ ሂደት ጥናት መሠረት ምላሽ የሚያስፈልጋቸው አዳዲስ የስራ መደቦች ሰለተፈጠሩ ተቋሙ በደንብ ቁጥር 99/2010 አንቀጽ 47 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡