የመመሪያ መለያ: 20/2013
ቀን: ነሐሴ 20፥ 2012 ዓ.ም.
Language: Amharic

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ዋና ር/መምህራንና ም/ር/መምህራን የድልድል አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 20/2013

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ የታየውን ለውጥ ለማስቀጠልና ዘላቂ ለማድረግ ለተማሪዎች የሚሰጠውን የመማር ማስተማር አገልግሎት ግልጽ፣ ፈጣንና ውጤታማ እንዲሆንና ተጠቃሚነትን ለማስፈን በርካታ የለውጥ ስራዎችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ከነዚህ ለውጦች መካከል ዋነኛው የከተማ አስተዳደሩን የመንግሥት ትምህርት ቤቶች አሠራር እንደገና በማዋቀር ተግባርና ሀላፊነታቸውን የሚመጥን መዋቅራዊ አደረጃጀትና የመሠረታዊ የስራ ሂደት ክለሳ ጥናት አካሂዷል፡፡

በዚህም መሠረት ለተዘጋጁ የስራ መደቦች ከመንግሥት ሰራተኞች አዋጅ ጋር የሚጣጣም የአፈፃፀም መመሪያና ቅደም ተከተልን መሠረት ያደረገ ጥናት ለየሥራ መደቦቹ በተሰጠው ደረጃ ዋና ርዕሰ መምህራንና ምክትል ር/መምህራንን መደቦች ላይ ብቃት ያላቸውን የትምህርት ቤት አመራሮች በውድድር ለመመደብ እንዲያስችል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ በመንግሥት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 56/2010 አንቀጽ 97 ንዑስ አንቀጽ 2 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን የዋና ርዕሰ መምህር እና ምክትል ርዕሰ መምህራን የድልድል አፈጻጸም መመሪያ አውጥቷል፡፡

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF

ተጨማሪ መረጃዎች

መመሪያውን ያውርዱ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ

Addis Ababa City Administration Public Service and Human Resource Development Bureau

Similar Directives

ሰኔ 1÷2018
የገቢዎች ሚኒስቴር
Ministry of Revenues
ሚያዝያ 8÷2018
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ
Addis Ababa City Administration Labor and Social Affairs Bureau
ሚያዝያ 8÷2018
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ
Addis Ababa City Administration Labor and Social Affairs Bureau
ሚያዝያ 8÷2018
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ
Addis Ababa City Administration Labor and Social Affairs Bureau