በተሽከርካሪ ምክንያት እየደረሰ ያለው አደጋ በየጊዜው እየጨመረ በመምጣት ላይ በመሆኑ፤
በተሽከርካሪ አደጋ ምክንያት የሚደርሰው የሰው ሞት፣ የአካል ጉዳትና የንብረት ኪሣራ ማህበራዊ ችግር የሚያስከትል በመሆኑ፤
የተሽከርካሪ አደጋ ተጎጂዎች አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት የሚያገኙበትን ስርዓት ማመቻቸትና የተሽከርካሪ ባለንብረቶች የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን ሽፋን እንዲኖራቸው ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ፤
በነባሩ የተሽከርካሪ አደጋ የሦስተኛ ወገን መድን አዋጅ አፈፃፀም የተለዩ ችግሮችና ያልተካተቱ ጉዳዮች በመኖራቸው እነዚህን እና ሌሎች ተያያዥ ድንጋጌዎችን ያካተተ ህግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ- መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•