በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የደረቅ ቆሻሻ አሰተዳደር ፕሮግራም የቆሸ-ረጲ የቆሻሻ ማስወገጃ መዝጊያ ምዕራፍ ፕሮጀክት ማስፍፀሚያ የሚውል መጠኑ 10 ሚሊዮን ዩሮ (አስር ሚሊዮን ዩሮ) የሚያስገኘው የብድር ስምምነት በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት እና በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ መካከል ታህሳስ 12 ቀን 2009 ዓ.ም በአዲስ አበባ የተፈረመ በመሆኑ፤
ይህንኑ የብድር ስምምነት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጥር 29 ቀን 2010 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 55 (1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።