ወጥነት ያለው፣ ውጤታማና ቀልጣፋ አገልግሎት የሚሰጥ፣ የሕዝብንና የመንግስትን ጥቅም በተሟላ ሁኔታ የሚያስጠብቅ አንድ ጠንካራ ሕግ አስከባሪ የዓቃቤ ሕግ ተቋም ማቋቋም አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
ሕጎች በሚገባ መደራጀታቸውንና የመንግስት ሥራዎች በሕግ መሠረት መመራታቸውን የሚያረጋግጥ እንዲሁም የሕግ የበላይነትን የሚያስከብር ተቋም እንደገና ማደራጀት አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ፤
የሕዝብ ተአማኒነት ያለው፣ በተሟላ ተቋማዊና ሙያዊ ነፃነት የሚያገለግል እንዲሁም ለሙያዊ፣ ተቋማዊና ሕዝባዊ ተጠያቂነት የሚገዛ፣ በግልጽነትና አሳታፊነት ሚሰራ የዓቃቤ ሕግ ተቋም ማደራጀት በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግስት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡