ሀብትን ማሳወቅና ማስመዝገብ የመንግሥት አሠራርን በግልጽነትና በተጠያቂነት ላይ ለመመስረት አስፈላጊ በመሆኑ፤
ሀብት ማሳወቅና ማስመዝገብ ሙስናና ብልሹ አሠራርን ለመከላከልና መልካም አስተዳደርን ለማስፈን ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ፤
የመንግሥት የሥራ ሃላፊነትና የግል ጥቅም ሳይቀላቀሉ በየራሳቸው መንገድ የሚመሩበትን ግልጽ ሥርዓት መዘርጋት ሊፈጠር የሚችለውን የጥቅም ግጭት ለማስወገድ እንደሚረዳ በመታመኑ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 55 (1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡