የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፌደራል የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2ሺ9 አንዳንድ አንቀጾች የአፈፃፀም ግልፅነት የሚጎድላቸው በመሆኑ፤
በአንዳንድ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች ላይ ጫናን ያሳደሩ የደንቡን አንቀጾች ማሻሻል በማስፈለጉ፤
ከዚህ በላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች ደንቡን ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በፌደራል የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2ሺ8 አንቀጽ 99 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህን ደንብ አውጥቷል፡፡
•