የመገናኛ አገልግሎት የአገሪቱ የኢኮኖሚና ማህበራዊ ልማት ወሳኝ ተግባር በመሆኑ፤
መንግስት የአገሪቱን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገት ለማሳደግ የቴሌኮሙኒኬሽን ገበያውን መልሶ ለማዋቀርና የቴሌኮሙኒኬሽን አገልግሎት አቅርቦት ላይ ተወዳዳሪነትን ለማስተዋወቅ በመወሰኑ፤
የመንግስት የቴሌኮሙኒኬሽን ገበያ መልሶ ማዋቀርና ተወዳዳሪነትን የማስተዋወቅ ፖሊሲን ለማሳካት ገለልተኛ፣ ግልጽነት ያለውና ተጠያቂነት ያለው የቁጥጥር ባለስልጣን ማቋቋም አስፈላጊ በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።