የተሻረ

የንግድ ምዝገባና ፍቃድ አዋጅ

በነጻ ገበያ የኢኮኖሚ ፖሊሲ መሠረት በማናቸውም የንግድ ሥራ መስክ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር አስፈላጊ ስለሆነ፤

የንግድ ሥራ ፈቃድ አሰጣጥና የምዝገባ ሥርዓት የነጻ ገበያ ኢኮኖሚን ለማራመድ በሚያስችል መልኩ እንዲሻሻል ማድረግና ሕጋዊ ሆኖ የተሰማራው ኅብረተሰብ በዚህ ረገድ የሚያጋጥሙትን መሰናክሎች ማስወገድ አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ፤

በአንድ በኩል ለሕጋዊ የንግድ ሥራ እንቅስቃሴዎች ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ተገቢ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ሕገ ወጥ እንቅስቃሴዎችን መግታት አስፈላጊ ስለሚሆን፤

እስከአሁን በተለያዩ መሥሪያ ቤቶች በተበታተነ ሁኔታ ሲከናወን የነበረውን የንግድ ሥራ ፈቃድ የመስጠት ተግባር በሥራዎቹ ልዩ ባህርይ ምክንያት በሌላ መሥሪያ ቤት እንዲሰጡ የግድ አስፈላጊ ከሆኑት በስተቀር ለአፈጻጸም በሚያመችና ከሞላ ጐደል በተጠቃለለ መልክ አግባብ ባላቸው የንግድና ኢንዱስትሪ ሴክተር መሥሪያ ቤቶች ብቻ መከናወን እንዳለበት ስለታመነበት፤

ቀደም ሲል ለነበሩ ሥርዓቶች እንዲያገለግሉ ተቀርጸው እስከ አሁን በሥራ ላይ የሚገኙ ሕጐች አንዳንድ ድንጋጌዎች በአሁኑ ወቅት ከምናራምደው የነጻ ገበያ ኢኮኖሚ ሥርዓት ጋር ስለማይ ጣጣሙ አስፈላጊውን ለውጥ ማድረግ ተገቢ ስለሆነና በተለያዩ አዋጆች ተበታትነው የሚገኙትን የምዝገባና የፈቃድ አሰጣጥ ድንጋጌዎች በአንድ አዋጅ አጠቃሎ ማውጣት አስፈላጊ ስለሆነ፤

በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ–መንግሥት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል።

PDF Document

Tap the button below to view or download this PDF.

View PDF

ተጨማሪ መረጃዎች

መለያ: አዋጅ ቁጥር 67/1989
ቀን: የካቲት 27፥ 1989 ዓ.ም.
Law Type: Proclamations

ሕጉን ያውርዱ

ተዛማጅ ሕጎች

ደንብ ቁጥር 126/1998

ሚያዚያ 27፥ 1998 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 95/1996

ህዳር 11፥ 1996 ዓ.ም.
የተሻረ
አዋጅ ቁጥር 376/1996

ህዳር 3፥ 1996 ዓ.ም.
የተሻረ
ደንብ ቁጥር 87/1995

ሐምሌ 15፥ 1995 ዓ.ም.
የተሻረ
ደንብ ቁጥር 37/1990

ሰኔ 12፥ 1990 ዓ.ም.
በአገልግሎት ላይ
ደንብ ቁጥር 13/1989

የካቲት 29፥ 1989 ዓ.ም.
የተሻረ