ቅርስ የሰው ልጅ የዕድገት ሂደት፣ ባህልና ታሪክ መገለጫ ስለሆነ ለዘላቂነቱ ጥበቃና እንክብካቤ የሚያደርግለትን አካል በህግ መወሰን አስፈላጊ በመሆኑ፤
ኅብረተሰቡን አሳታፊ ያደረገ የቅርስ አስተዳደር ሥርዓት በመዘርጋት ቅርሶች ላሉበት አካባቢ ኅብረተሰብ ብሎም ለሀገር አቀፍ ዘላቂ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማት ከፍተኛ አስተዋፅዖ እንዲያበረክቱ ማስቻል አስፈላጊ በመሆኑ፤
የሀገሪቱን ቅርሶች በዓለም ቅርስ መዝገብ ዝርዝር ውስጥ ለማስገባት የሚያስችሉ የዝግጅት ሥራዎችን ለማከናወን በቅድሚያ ቅርሶችን በደረጃ መመደብ በማስፈለጉ፤
የቅርሶች አስተዳደርን በሚመለከት የሥራ መደራረብና የሃብት ብክነት እንዳይፈጠር በፌደራልና በክልሎች መካከል የሚኖረውን የኃላፊነት ድርሻ መለየት እና ቀልጣፋ የአስተዳደርና የአሰራር ስርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፤
ስለቅርስ ጥናትና አጠባበቅ በወጣው አዋጅ ቁጥር 209/1992 አንቀጽ 16 ላይም ቅርሶች በብሔራዊና በክልል ደረጃ የሚመደቡበት አግባብ በሕግ እንደሚወሰን የተደነገገ በመሆኑ፤
በኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 55(1) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡
•
•
•
•
•
•
•
•
•