ማስታወቂያ ሕብረተሰቡ በምርት ግብይት ወይም በአገልግሎት አሰጣጥ ረገድ በሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ላይ ተጽእኖ በማሳደር ለአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ እድገት ከፍተኛ ሚና የሚጫወት በመሆኑ፤
አገሪቱ በገበያ መር የኢኮኖሚ ሥርዓት የምትመራ ከመሆኑ አንጻር ገበያው ጤናማ በሆነ ውድድር እንዲመራ በማድረግ ረገድ ማስታወቂያ ከፍተኛ አስተዋፆ የሚያደርግ በመሆኑ፤
ማስታወቂያ በሥርዓት ካልተመራ የሕብረተሰቡን መብትና ጥቅም እንዲሁም የአገርን ገጽታ ሊጎዳ የሚችል በመሆኑ፤
የማስታወቂያ ወኪሎች፣ የማስታወቂያ አሰራጮች እና የማስታወቂያ አስነጋሪዎችን መብት እና ግዴታን በግልጽ መወሰን በማስፈለጉ፤
በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት አንቀጽ 55 (1) መሰረት የሚከተለው ታውጇል፡፡