የታክስ ሒሳብ መዝገብ የመያዝ ግዴታ የተጣለበት ግብር ከፋይ የሚይዘው የሂሳብ መዝገብ ሊያሟላ የሚገባውን ዝርዝር ሁኔታ በነባሩ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ በግልጽ ስላልተቀመጠ በአግባቡ መደንገግ ስላለበት፤
ስለ ሰነድ አቀራረብ ወይም ሰነድ ተሟልቶ ባልቀረበ ጊዜ ሊኖር ስለሚገባው አሠራርበግልጽ ለማስቀመጥ እና በሁሉም የታክስ ባለስልጣኑ ቅ/ጽ/ቤቶች የታክስ ሒሳብ መዝገብ አያያዝን በተመለከተ ተመሳሳይ ግንዛቤ እንዲኖር በማስፈለጉ፤
ግብር ከፋዩ ከሚይዘው የታክስ ሂሳብ መዝገብ ጋር ተያይዘው መቅረብ ያለባቸውን ሰነዶች በዝርዝር ማመላከት እና የመመሪያው ወሰን በታክስ ሕግ መሠረት እንዲመራ ማድረግ በማስፈለጉ፤የገቢዎች ሚኒስቴር በፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 979/2008 አንቀጽ 82(7) እና በፌዴራል የገቢ ግብር ደንብ ቁጥር 410/2009 አንቀጽ 58(1) ላይ በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህን መመሪያ አውጥቷል፡፡