ለዜጎች የስራ ዕድል በመፍጠር እንዲሁም ኢንተርፕራይዞች የሚቋቋሙበትንና የሚደገፉበትን ፖሊሲና ስትራቴጂ በማውጣት በተግባርላይ እንዲውልበማድረግ በከተማችን የሚታየውን የድህነትና የስራ አጥነት ችግሮችን በዘላቂነት በመቅረፍ የከተማዋን ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ እሴቶች ማሳደግ በማስፈለጉ፤
በመሆኑም በዘርፉ የሚታዩትን ብልሹ የሆኑ አሰራሮችን ለመቅረፍ፤ የግልጽነትና ተጠያቂነት አሠራር ሥርዓትን ለመዘርጋት ያመች ዘንድ የስራ ዕድል ፈጠራ እና የኢንተርፕራይዞች የአደረጃጀት መመሪያን ማዘጋጀትና በተግባር ላይ ማዋል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ፣ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላት ሥልጣና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 74/2014 አንቀጽ 15 ንዑስ አንቀጽ (2) ተራ ፊደል (ሠ) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡