የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ገንዘቦችን እንዲሁም ወርቅን ከተፈቀደው መጠን በላይ ህገወጥ በሆነ እና ባልተገባ መልኩ ይዞ የመገኘት እና የማዘዋወር ስጋት እንዲሁም ተግባራዊ እንቅስቃሴ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ፣
ወርቅ፤ ህገወጥ ገንዘብ፣ እንዲሁም ሀሰተኛ የገንዝብ ኖት ይዞ ከመገኘት እና ከማዘዋወር ጋር በተያያዘ እንዲሁም ህገወጥ በሆነ መንገድ ያለፈቃድ ገንዘብ የማስተላለፍ የሀዋላ ስራ ጋር በተያያዘ የሚፈጸሙ ወንጀሎችን በተገቢው መንገድ እና በመረጃ በመታገዝ መቆጣጠር አስፈላጊ በመሆኑ እና ለዚህም አስተዋጽኦ ለሚያደርጉ ጠቋሚዎች እና ያዦች ከተግባራቸው ጋር የተመጣጠነ የማበረታቻ ወሮታ ሊከፈላቸው የሚገባ በመሆኑ፣
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ማቋቋሚያ(እንደተሻሻለ) አዋጅ ቁጥር 591/2000 አንቀጽ 21(5(ለ) እና አንቀጽ 27(2) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ይህንን መመሪያ አውጥቷል፡፡