የታክስ አስተዳደር ስርዓቱን በማጠናከር ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በብቃት ለመሰብሰብ እና ለተገልጋዩ የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት እንዲቻል በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣንና በአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ባለሥልጣን በተናጠል ሲከናወን የነበረው የግብር /ታክስ/ እንዲሁም የማዘጋጃ ቤት ገቢዎች አሰባሰብ በአንድ ተቋም እንዲከናወን ተወስኗል፡፡
በዚህም መሠረት የአዲስ አበባ አስተዳደር እና የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መስከረም 25 ቀን 2003 ዓ.ም ባደረጉት የሁለትዮሽ የመግባቢያ ስምምነት መሠረት በአዲስ መልክ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ከግብር ከፋዮች ግብር/ታክስ እና የማዘጋጃ ቤት ገቢዎች ሲሰበስቡ እንዲሁም የተሰበሰውን ገቢ ለገቢው ባለድርሻ ሲያስተላልፉ የሂሳብ አመዘጋገቡ የሚመራበትን ስርዓት ለመወሰን የአዲስ አበባ አስተዳደር እና የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መስከረም 25 ቀን 2003 ዓ.ም ባደረጉት የሁለትዮሽ የመግባቢያ ስምምነት አንቀጽ 4/2 ፊደል ተራ (ሠ) እና (ሰ) መሠረት ይህ መመሪያ ወጥቷል፡፡