የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ነዋሪዎች ህይወትና ንብረት እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ደኅንነት ከማንኛውም አደጋዎች እንዲጠበቅ ማድረግና አስተማማኝ የሥራና የመኖሪያ አካባቢ ለመፍጠር፤
ከተቋማት ጋር ያለውን የስራ ትስስርና ግንኙነት ሥርዓት ባለው መልኩ አጠናክሮ ለማስኬድና የአፈፃፀም ሁኔታዎችን ለመከታተል የሚያስችል አመቺ ሁኔታዎችን በመፍጠር የኃላፊነትና የተጠያቂነት ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ፤
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዉስጥ የሚገኙ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን ደኅንነት ዝርዝር አፈጻጸምና የአሠራር ሂደቶችን ለመከታተል የሚያስችል ግልፅ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ የሆነ የአሠራር ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈጻሚ አካላትን ሥልጣን እና ተግባር እንደገና ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁጥር 84/2016 አንቀጽ 16 (2) (ሠ) እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአደጋ ስጋት ደኅንነት ደንብ ቁጥር 132/2014 አንቀጽ 25 መሠረት ኮሚሽኑ ይህንን መመሪያ አውጥቷል።