የፍትሕ ሚኒስቴር በአዋጅ ቁጥር 1249/2013 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፡-
1. የፌደራል ጠበቆች እና የጥብቅና ድርጅቶች የሥነ-ምግባር ጥስት የጥቆማ አቀራረብ፣ የምርመራ እና የውሳኔ አሰጣጥ ረቂቅ መመሪያ እና
2. የእድሳት ጊዜው ያለፈ የጥብቅና ፈቃድ ላይ የሚጣል የገንዘብ ቅጣት መጠን መወሰኛ ረቂቅ መመሪያ አዘጋጅቷል፡፡
አስተያየት መስጠት የሚፈልግ ማንኛውም ሰው የረቂቆቹን ቅጂ ከዚህ በታች የተመለከተውን ሊንክ በመጫን ማግኘት የሚችል ሲሆን እስከ ታህሳስ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ በኢ-ሜይል አድራሻ [email protected] እንድትልኩ ወይም በዋና መ/ቤት የጥብቅና ፍቃድ አስተዳደርና ነፃ የሕግ ድጋፍ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በጽሁፍ እንድትሰጡ እንጠይቃለን፡፡
የእድሳት_ጊዜው_ያለፈ_የጥብቅና_ፈቃድ_ላይ_የሚጣል_የገንዘብ_ቅጣት_መጠን_መወሰ…” https://shorturl.at/sPSgW
የሥነ_ምግባር_ጥስት_የጥቆማ_አቀራረብ፣_የምርመራ_እና_የውሳኔ_አሰጣጥ_ረቂቅ_መመሪያ https://shorturl.at/GyNx5